ሰቆቃው ኤርምያስ 3:1-64
Ethiopian Amharic Bible (AMH)
1አሌፍ። በቍጣው በትር መከራ ያየ ሰው እኔ ነኝ።
2ብርሃን ወደ ሌለበት ወደ ጨለማ መርቶ ወሰደኝ።
3ዘወትር ቀኑን ሁሉ እጁን በላዬ መለሰ።
4ቤት። ሥጋዬንና ቁርበቴን አስረጀ፥ አጥንቴን ሰበረ።
5ቅጥር ሠራብኝ በሐሞትና በድካምም ከበበኝ።
6ቀድሞ ሞተው እንደ ነበሩ በጨለማ አኖረኝ።
7ጋሜል። እንዳልወጣ በዙሪያዬ ቅጥር ሠራብኝ፤ ሰንሰለቴን አከበደ።
8በጠራሁና በጮኽሁ ጊዜ ጸሎቴን ከለከለ።
9መንገዴን በተጠረበ ድንጋይ ዘጋ፥ ጐዳናዬንም አጣመመ።
10ዳሌጥ። እንደሚሸምቅ ድብ እንደ ተሸሸገም አንበሳ ሆነብኝ።
11መንገዴን ለወጠ፥ ገነጣጠለኝም፤ ባድማ አደረገኝ።
12ቀስቱን ገተረ ለፍላጻውም እንደ ጊጤ አደረገኝ።
13ሄ። የሰገባውን ፍላጻዎች በኵላሊቴ ውስጥ ተከለ።
14ለወገኔ ሁሉ ማላገጫ ቀኑንም ሁሉ መሳለቂያ ሆንሁ።
15ምሬት ሞላብኝ በእሬትም አጠገበኝ።
16ዋው። ጥርሴን በጭንጫ ሰበረ፥ በአመድም ከደነኝ።
17ነፍሴን ከሰላም አራቅህ፤ በጎ ነገርን ረሳሁ።
18እኔም። ኃይሌ ከእግዚአብሔርም ዘንድ ያለው ተስፋዬ ጠፋ አልሁ።
19ዛይ። መከራዬንና ችግሬን እሬትንና ሐሞትን አስብ።
20ነፍሴ እያሰበችው በውስጤ ፈዘዘች።
21ይህችን በልቤ አኖራለሁ፥ ስለዚህ እታገሣለሁ።
22ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና።
23ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።
24ነፍሴ። እግዚአብሔር እድል ፈንታዬ ነው፤ ስለዚህ ተስፋ አደርገዋለሁ አለች።
25ጤት። እግዚአብሔር በተስፋ ለሚጠብቁት ለምትሻውም ነፍስ መልካም ነው።
26ሰው ዝም ብሎ የእግዚአብሔርን ማዳን ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው።
27ሰው በታናሽነቱ ቀንበር ቢሸከም መልካም ነው።
28ዮድ። እርሱ አሸክሞታልና ዝም ብሎ ለብቻው ይቀመጥ።
29ተስፋ የሆነው እንደ ሆነ አፉን በአፈር ውስጥ ያኑር።
30ጕንጩን ለሚመታው ይስጥ፥ ስድብንም ይጥገብ።
31ካፍ። ጌታ ለዘላለም አይጥልምና፤
32ቢያሳዝንም እንደ ምሕረቱ ብዛት ይራራልና፤
33የሰውን ልጆች ከልቡ አያስጨንቅም፥ አያሳዝንምም።
34ላሜድ። በምድር የተጋዙትን ሁሉ ከእግሩ በታች ይረግጣቸው ዘንድ፥
35የሰውን ፍርድ በልዑል ፊት ይመልስ ዘንድ፥
36የሰውን ፍርድ ያጣምም ዘንድ ጌታ እሺ አይልም።
37ሜም። ጌታ ያላዘዘውን የሚልና የሚፈጽም ማን ነው?
38ከልዑል አፍ ክፉና መልካም ነገር አይወጣምን?
39ሕያው ሰው የሚያጕረመርም፥ ሰው ስለ ኃጢአቱ ቅጣት የሚያጕረመርም ስለ ምንድር ነው?
40ኖን። መንገዳችንን እንመርምርና እንፈትን፥ ወደ እግዚአብሔርም እንመለስ።
41ልባችንን ከእጃችን ጋር በሰማይ ወዳለው ወደ እግዚአብሔር እናንሣ።
42በድለናል ዐምፀናልም፥ አንተም ይቅር አላልህም።
43ሳምኬት። በቍጣ ከደንኸን አሳደድኸንም፤ ገደልኸን፥ አልራራህም።
44ጸሎት እንዳያልፍ ራስህን በደመና ከደንህ።
45በአሕዛብ መካከል ጕድፍና ውዳቂ አደረግኸን።
46ዔ። ጠላቶቻችን ሁሉ አፋቸውን ኣላቀቁብን።
47ድንጋጤና ቍጣ፥ ጥፋትና ቅጥቃጤ ሆነብን።
48ስለ ወገኔ ሴት ልጅ ቅጥቃጤ ዓይኔ የውኃ ፈሳሽ አፈሰሰች።
50ስለ ከተማዬ ቈነጃጅት ሁሉ ዓይኔ ነፍሴን አሳዘነች።
51ጻዴ። በከንቱ ነገር ጠላቶች የሆኑኝ እንደ ወፍ ማደንን አደኑኝ።
52ሕይወቴን በጕድጓድ አጠፉ፥ በላዬም ድንጋይ ጣሉ።
53በራሴ ላይ ውኆች ተከነበሉ፤ እኔም። ጠፋሁ ብዬ ነበር።
54ቆፍ። አቤቱ፥ በጠለቀ ጕድጓድ ውስጥ ሆኜ ስምህን ጠራሁ።
55ድምፄን ሰማህ፤ ጆሮህን ከልመናዬ አትመልስ።
56በጠራሁህ ቀን ቀርበህ። አትፍራ አልህ።
57ሬስ። ጌታ ሆይ፥ ስለ ነፍሴ ተምዋግተህ ሕይወቴን ተቤዠህ።
58አቤቱ፥ ጭንቀቴን አይተሃል፥ ፍርዴን ፍረድልኝ።
59በቀላቸውን ሁሉና በእኔ ላይ ያለውን አሳባቸውን ሁሉ አየህ።
60ሳን። አቤቱ፥ ስድባቸውንና በእኔ ላይ ያለውን አሳባቸውን ሁሉ፥
61የተነሡብኝን ሰዎች ከንፈሮች ቀኑንም ሁሉ ያሰቡብኝን አሳባቸውን ሰማህ።
62መቀመጣቸውንና መነሣታቸውን ተመልከት፤ እኔ መሳለቂያቸው ነኝ።
63ታው። አቤቱ፥ እንደ እጃቸው ሥራ ፍዳቸውን ትከፍላቸዋለህ።
64የልብ ዕውርነትንና እርግማንህን ትሰጣቸዋለህ።
65አቤቱ፥ በቍጣ ታሳድዳቸዋለህ ከሰማይም በታች ታጠፋቸዋለህ።